Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ኦማር ጊሌህ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 5 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ባለፈው ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በተካሄደው ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት ለመመስረት የሚያስችልዎትን ድምጽ በማግኘትዎ እንኳን ደስ አለዎት ብለዋል፡፡

በመልዕክታቸውም “በእርስዎ መሪነት ወዳጅ የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ በረጅም ጊዜ የሚበለጽግና ዘመናዊ ዕሴቶችን የሚቀበል ማህበረሰብ ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት ለዓለም እያሳየ ይገኛል” ይገኛል ማለታቸውን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.