Liege Airport, August 2009 Refueling. Tank truck. © Pierre Havrenne / Pachacamac

ቢዝነስ

አየር መንገዱ ከሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር በጭነት አገልግሎት ያለውን ውል አራዘመ

By Tibebu Kebede

July 15, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 8 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቤልጂየሙ ሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር በጭነት አገልግሎት ያለውን ውል ለተጨማሪ አመታት አራዘመ፡፡

አየር መንገዱ ከአውሮፕላን ማረፊያው ጋር ለቀጣዮቹ አምስት አመታት ነው ውሉን ያራዘመው፡፡

በዚህም የሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ እና አውሮፓ መካከል የጭነትና የሎጂስቲክስ አገልግሎት መተላለፊያ ሆኖ እንደሚያገለግል የኤር ካርጎ መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 15 አመታት ከሌጅ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር በመተባበር በአውሮፓ የተሳካ የጭነት አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!