Fana: At a Speed of Life!

በመተከል ዞን ከ5 ሚሊየን በላይ ችግኞች እየተተከሉ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 9 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ5 ሚሊየን በላይ ችግኞች እየተተከሉ ነው፡፡

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የመተከል ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበበ እንድሪስ እንደገለፁት በዚህ ዓመት በዞኑ በሚገኙ አራት ወረዳዎች 5 ሚሊየን 500 ሺህ ለምግብነት የሚውሉ ምጣኔ ሃብታዊ ጠቀሜታ ያላቸው እና ሀገር በቀል የሆኑ ችግኞች ይተከላሉ፡፡

ኃላፊው እስካሁን በዳንጉር እና ፓዊ ወረዳዎች ከ250 ሺህ በላይ ችግኞች መተከላቸውን ጠቁመዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ72 ሚሊየን በላይ ችግኞች ለመተከል ዝግጅት መደረጉም ታውቋል።

በዘንድሮው ”የኢትዮጵያን እናልብሳት” የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በመላ ሃገሪቱ ከ6 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ተግባራዊ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ እንደሚገኝም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.