ምክር ቤቱ በነገው ዕለት የሲቪል አቪየሽን አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ያፀድቃል
አዲስ አበባ፣ ጥር 18 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ በነገው እለት ይካሄዳል።
ምክር ቤቱ በነገው በስብሰባው የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የ2012 በጀት ዓመት የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ያደምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ከዚህ ባለፈም የሲቪል አቪየሽን አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ እንደሚያፀድቅ ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።