የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በዋሽንግተን እየተወያዩ ነው

By Tibebu Kebede

January 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በዋሽንግተን ዲሲ እየተወያዩ ነው።

በውይይቱ ላይ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ጨምሮ የግብፅ እና የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የውሃ ሚኒስትሮች፣ የውኃ ዘርፍ እና የህግ ባለሙያዎች ዋሽንግተን ዲሲ ተገኝተዋል።