የሀገር ውስጥ ዜና

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የሰላም ኮንፈረንስ ተካሄደ

By Tibebu Kebede

January 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደቱን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማካሄድ እንዲቻል በዛሬው እለት የሰላም ኮንፈረንስ አካሄደ።

በኮንፈረንሱ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ አባ ገዳዎች፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ተማሪዎችና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።