ቢዝነስ

የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

By ዮሐንስ ደርበው

July 28, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 21 ፡ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡

በምግብ ደህንነት ስራ አመራር ትግበራ ላይ የምክር አገልግሎት ለመስጠት ፑራቶል ኢትዮጵያ የምግብ ኢንዱስትሪ ከተባለ ኩባንያ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳለው መኮንን እና ፑራቶል ኢትዮጵያ የምግብ ኢንዱስትሪ ዋና ዳይሬክተር ተፈራርመውታል፡፡

ስምምነቱ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ሲሆን አፈፃፀሙን በመገምገም እየተሻሻለ እንደሚሄድ መገለጹን ከኤጀንሲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡