ስፓርት

ለሜቻ ግርማ እና ጌትነት ዋለ በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል የፍፃሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋገጡ

By Feven Bishaw

July 30, 2021

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 23፣ 2013 ( ኤፍ ቢ ሲ) ሌሊት ላይ በተካሄደው የቶኪዮ 2020 አትሌቲክስ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ወንዶች ማጣሪያ እንዲሁም የ800 ሜትር የሴቶች ማጣሪያ ውድድሮች ተሳትፈዋል፡፡

በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ወንዶች ማጣሪያ ለሜቻ ግርማ በ8 ደቂቃ 9 ሰከንድ ከ83 ማይክሮ ሰከንድ ሰዓት 1ኛ እንዲሁም ጌትነት ዋለ በ8 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ከ55 ማይክሮ ሰከንድ 2ኛ ሆኖ በመግባት ማጣሪያውን አልፈዋል፡፡