አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ መርሃ ግብር አስጀምሯል፡፡
በቢሮው የአስተዳደር ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ከበደ÷እኛ ኢትዮጵያውያን እርሳ በርስ መረዳዳትና መደጋገፍ ባሕላችን በመሆኑ በዘርና በሃይማኖት ሳንከፋፈል ሕብረ ብሔራዊ ሀገር መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡