አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 25፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ገንዘብ ለማሰባሰብ ታስቦ በተሰራው ዘመናዊ የሃብት ማሰባሰቢያ ሥርዓት አማካኝነት 132 ሺህ ዶላር ተሰበሰበ።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ፅህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሃይሉ አብረሃ እንደተናገሩት÷ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ዜጎች ለግድቡ ድጋፍ ማድረጋቸው ተጠናክሮ ቀጥሏል።