የሀገር ውስጥ ዜና

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ከ132 ሺህ ዶላር በላይ ተሰበሰበ

By Feven Bishaw

August 01, 2021

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 25፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ገንዘብ ለማሰባሰብ ታስቦ በተሰራው ዘመናዊ የሃብት ማሰባሰቢያ ሥርዓት አማካኝነት 132 ሺህ ዶላር ተሰበሰበ።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ፅህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሃይሉ አብረሃ እንደተናገሩት÷ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ዜጎች ለግድቡ ድጋፍ ማድረጋቸው ተጠናክሮ ቀጥሏል።