የሀገር ውስጥ ዜና

አየር መንገዱን በተመለከተ የሚናፈሱ ወሬዎች መሰረተ ቢስ ናቸው-የኢትዮጵያ አየር መንገድ

By Feven Bishaw

August 01, 2021

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 25፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጦር መሳሪያ ወደ ትግራይ ክልል እያጓጓዘ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ ሃሰተኛ መሆኑን አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ ይህን በተመለከተ ባወጣው መግለጫ ÷ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጦር መሳሪያ ወደ ትግራይ ክልል እያጓጓዘ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ በአንዳንድ ግለሰቦች የሚናፈሰውን ወሬ ውድቅ አድርጓል፡፡