የሀገር ውስጥ ዜና

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ3 ሺህ 176 በላይ ተማሪዎቹን አስመረቀ

By Melaku Gedif

August 07, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ከ3 ሺህ 176 በላይ ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

በተጨማሪም የዩኒቨርስቲው የትምህርት ሴኔት ለ5 ምሁራን የረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መስጠቱ ነው የተገለጸው፡፡