የሀገር ውስጥ ዜና

የፕላንና ልማት ኮሚሽን እና የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን በዲጂታል ክትትልና ሪፖርት አቀራረብ ሥርዓት ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አደረጉ

By Melaku Gedif

August 07, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕላንና ልማት ኮሚሽን ከአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ጋር በዲጂታል የክትትልና ሪፖርት አቀራርብ ሥርዓት ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።

የልምድ ልውውጡ ጠቃሚ አሰራር ዘዴዎችን ከአንዱ ወደሌላው ለማስተላፍ እንዲሁም የሚኖሩ ጉድለቶችን እና ክፍተቶችን ለመሙላት የታሰበ እንደሆነ ተገልጿል፡፡