የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮ ጀርመን የሚኒስትሮች ኮሚሽን የባለሙያች የምክክር መድረክ ተጠናቀቀ

By Tibebu Kebede

January 30, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ ጀርመን የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን የባለሙያች የምክክር መድረክ ተጠናቋል።

በውይይት መድረኩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2011 ዓ.ም በበርሊን በተፈራረሙት የጋራ ኮሚሽን ስምምነት መሰረት እና የሀገራቱን የጋራ ፍላጎት መሰረት ያደረጉ አዳዲስ የትብብር መስኮችን መጀመር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።