የሀገር ውስጥ ዜና

ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ከታገቱ ተማሪዎች ወላጆች ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

January 30, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች በቅርቡ ከታገቱት የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወላጆች ጋር ተወያዩ።

በውይይቱም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የሰላም ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚልና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች በተጨማሪ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተማሪዎቹ የትውልድ ቦታ ተወካዮች ተሳትፈዋል።