አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ክልል የውኃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ግንባታቸው በ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የሚካሄድ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የኮንትራት ውል ስምምነት ከስራ ተቋራጮች እና አማካሪዎች ጋር ተፈራረመ።
የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ በ13 ዞኖች ውስጥ የሚካሄዱ ሲሆን፥ በዚህም 12 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እና 53 የጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ ፕሮጀክቶች እንደሚካሄዱም ነው የተገለፀው።