የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ በ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የሚካሄዱ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የኮንትራት ስምምነት ተፈረመ

By Tibebu Kebede

January 30, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ክልል የውኃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ግንባታቸው በ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የሚካሄድ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የኮንትራት ውል ስምምነት ከስራ ተቋራጮች እና አማካሪዎች ጋር ተፈራረመ።

የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ በ13 ዞኖች ውስጥ የሚካሄዱ ሲሆን፥ በዚህም 12 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እና 53 የጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ ፕሮጀክቶች እንደሚካሄዱም ነው የተገለፀው።