Fana: At a Speed of Life!

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለተቋሙ ስኬት ጥረት ላደረጉ አካላት የእውቅና መርሃ ግብር እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የ2021 የሄርት ኮንቬንሽን ተሸላሚው ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለተቋሙ ስኬት ያለሰለሰ ጥረት ላደረጉ ሰራተኞች፣ ተቋማት እና ግለሰቦች የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደዉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ምርምር፣ የቴክኖሎጂ እና ኢንዱስትሪ ትስስር ኮንቬንሽን አሸናፊ መሆኑን ምክንያት በማድረግ የምስጋና እና የእውቅና አሰጣጥ መርሃግብር እያካሄደ ነው፡፡

በመርሀ ግብሩ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ ለተገኘው ስኬት የእንኳን ደስ አላቹህ መልዕክት አስተላልፈው÷ ተቋሙ ከ12ቱ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች በአፈፃፀም፣ በአመራርና በፈጠራ አሸናፊ እንዲሆን ከፅዳትና ከውበት ሰራተኞች እስከ ከፍተኛ የተቋሙ አመራሮች ሁሉም የበኩሉን ጠጠር በማቀበሉ ነው ብለዋል።

የተኘውን ስኬት ከመዘከር ባሻገር እንዴት ማስቀጠል ይቻላል በሚለው ጉዳይ ላይ የተገኙ ስኬቶች፣ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው።

የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብዱላኪም ሙሉ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት÷ የሐይማኖት አባቶች ፣ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ፣መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የተቋሙ ሰራተኞች ተገኝተዋል።

በወርቃአፈራው ያለው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.