የሀገር ውስጥ ዜና

በጅማ ከተማ በባለሀብቶችና በበጎ ፍቃደኞች 89 የመማሪያ ክፍሎች ተገነቡ

By Feven Bishaw

August 27, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅማ ከተማ በዚህ አመት በባለሀብቶችና በበጎ ፍቃደኞች በ44 ሚሊየን ብር ወጪ 89 የመማሪያ ክፍሎች መገንባታቸው ተገለፀ።

ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠልም በቀጣይ አመት በ102 ሚሊየን ብር 12 የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን ለማስገንባት ታቅዶ ዛሬ የዲዛይንና የካርታ ርክክብ ተደርጓል።