የሀገር ውስጥ ዜና

ኤሌክትሪክ አገልግሎት 58 ሚሊየን ዶላር የፈጀ ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ መተግበሪያ አስመረቀ

By Tibebu Kebede

February 01, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ58 ሚሊየን ዶላር ወጪ ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ መተግበሪያ ፕሮጀክት አስመረቀ።

ኢ.አር.ፒ /ኢንተርፕራይዝ ሪሶስር ፕላኒንግ/ የተሰኘው ይህ መተግበሪያ የተቋሙን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ከማሳደግ ባሻገር ለተገልጋዮች ቀልጣፋ፣ ግልፅና ተጠያቂነት ያለው አገልግሎት መስጠት ያስችላል ተብሏል።