የሀገር ውስጥ ዜና

ዩኔስኮ ዓለም አቀፋዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት ልዩ መለያው ነው- ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ

By Tibebu Kebede

February 01, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመንግስታቱ ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ማዕከል (ዩኔስኮ)ዓለም አቀፋዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት ልዩ መለያው መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ገለፁ።

የትምህርትን በጎ አስተዋጽዎ እንደገና መቅረጽና ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክረ ሀሳብ የሚያቀርበው ዓለም ዓቀፍ ኮሚሽን በፈረንሳይ ፓሪስ ስብሰባውን ባደረገበት ወቅት ነው ፕሬዚዳንቷ ይህንን የገለፁት።