የሀገር ውስጥ ዜና

አሁን ገንዘብ ሳይሆን ሀገር እና ህዝብ የምናተርፍበት ጊዜ ነው- ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

By Feven Bishaw

August 31, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የሚስተዋለውን የኢኮኖሚ አሻጥርና ህገወጥ ተግባራት ለመከላከልና ለመቆጣጠር በስራ ላይ ያለው የቁጥጥር ግብረሃይል የስራ አፈጻጸም ተገመገመ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የቁጥጥር ግብረሃይሉ ሰብሳቢ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ግብረሃይሉ ባለፉት ቀናት ባካሄደው የክትትል እና የቁጥጥር ስራዎች በአጠቃላይ የግብይት ስርዓቱን ማረጋጋት ተችሏል ብለዋል፡፡