የሀገር ውስጥ ዜና

በአገው ግምጃ ቤት ለሁለተኛ ዙር የሰለጠኑ ሚሊሻዎች ተመረቁ

By Feven Bishaw

September 01, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳደር ለሁለተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ሚሊሻዎች አስመረቀ፡፡

ሚሊሻዎቹ የክልሉ መንግስት ያቀረበውን የክተት ጥሪ ተከትሎ ለህልውና ዘመቻ ለመቀላቀል ለሁለተኛ ዙር ለ15 ቀናት መሠረታዊ የውትድርና ሙያ የሰለጠኑ ናቸው፡፡