የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ክልል በርካታ የሚሊሻ አባላት ወታደራዊ ስልጠና በመከታተል ላይ ይገኛሉ

By Feven Bishaw

September 01, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በማንኛውም ሰዓት ለሚደረግ ሀገራዊ ጥሪ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በርካታ የሚሊሻ አባላት ወታደራዊ ስልጠና በመከታተል ላይ እንደሚገኙ የደቡብ ክልል ሚሊሻ ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የክልሉን ሰላም ከማስጠበቅ ባለፈ የሀገርን ሉአላዊነት ለማረጋገጥ ፈቃደኛ የሆኑ የሚሊሻ አባላት ናቸው ወታደራዊ ስልጠናውን በመከታተል ላይ የሚገኙት።