የሀገር ውስጥ ዜና

በጎንደር ከተማ ህገ-ወጥ የነዋሪነት መታወቂያ ሲያዘጋጁ የነበሩ አራት ተጠርጣሪዎች ተያዙ

By Feven Bishaw

September 01, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ በአንድ የግል ማተሚያ ድርጅት ውስጥ በህገ-ወጥ መንገድ የተዘጋጁ 544 መታወቂያዎችን ከአራት ተጠርጣሪ ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የከተማው የሰላምና ደህንነት መምሪያ አስታወቀ፡፡

የመምሪያው የመረጃና ክትትል ባለሙያ አቶ ስንታየሁ ተገኘ እንደተናገሩት ህገ-ወጥ መታወቂያዎቹ የተያዙት በማተሚያ ድርጅቱ ውስጥ በተደረገ ድንገተኛ ቁጥጥር ነው፡፡