ስፓርት

በፕሪምየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ስሑል ሽረ፣ አዳማ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ድል ቀንቷቸዋል

By Tibebu Kebede

February 02, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 12ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት በተለያዩ ከተሞች ተካሂደዋል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሲዳማ ቡና በአዲስ አበባ ስታዲየም ባካሄዱት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ 6 ለ 2 በሆነ ሰፊ ልዩነት አሸንፏል።