አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያን የውስጥ አንድነት አደጋ ላይ ለመጣል የተነሱ ቡድኖችን ለመመከት ያለልዩነት መስራት ይገባል ሲሉ ምሁራን ተናገሩ።
የፍልስፍና መምህሩ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ፥ የለውጡ መንግስት በፈተናዎች ውስጥ ሆኖ የታላቁ የኢትዮጵያን ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትን ማሳካቱ፣ ለምዕራባውያን የማይጠመዘዝ አቅም መገንባት መቻሉ፣ ሀገር አቀፍ ምርጫን በስኬት ማካሄድ መቻሉ እንዲሁም የዲሞክራሲ ምህዳርን ለማስፋት መቻሉን በአድናቆት ጠቅሰዋል።