ቢዝነስ

የጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር 450 ሚሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ

By Meseret Demissu

September 02, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2013 በጀት ዓመት የጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ 450 ሚሊየን ብር መሰብሰቡን እና በ2014 517 ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱን አስታወቀ፡፡

በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ አቶ ሂርሲ አብዲ ለሶማሌ ክልል ቴሌቪዥን እንደገለፁት፥ በከተማው በ2013 የበጀት አመት ስድስት መቶ ዘጠኝ ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ አራት መቶ ሀምሳ ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ መቻሉን አስታውቋል።