የሀገር ውስጥ ዜና

በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ሼክ ሀሰን የበሬ ሪፈራል ሆስፒታል የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመረቀ

By Feven Bishaw

September 03, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ ሼክ ሀሰን የበሬ ሪፈራል ሆስፒታል የኩላሊት እጥበት ማዕከልን መርቀው ከፈቱ፡

ማዕከሉ በ27 ሚልየን ብር ወጪ የተገነባ ሲሆን÷ወጪው በዲያስፖራ ወጣቶች በራስ ተነሳሽነት፣ ከህዝቡ በተሰበሰበ እንዲሁም በክልሉ መንግሥት የተሸፈነ ነው፡፡