የሀገር ውስጥ ዜና

የዲጂታል ኢኮኖሚ ልማትን መደገፍ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈረመ

By Melaku Gedif

September 03, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ልማትን መደገፍ የሚያስችል የትብብር ስምምነት በኢትዮጵያና በጀርመን መካከል ተፈረመ።

ስምምነቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማእቀፍ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት እና ፖሊሲን ለመደገፍ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡