የሀገር ውስጥ ዜና

የአሶሳ ከተማ ሴቶች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሠልፍ አካሄዱ

By Feven Bishaw

September 03, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በአሶሳ ከተማ የተለያዩ የሴት አደረጃጀቶችና የከተማው ሴቶች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሠልፍ ዛሬ አካሂደዋል።

የከተማው ሴቶች ባካሄዱት ሠልፍ አሸባሪውን የህወሓትን ቡድን የሚያወግዙና ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ድጋፋቸውን የሚያረጋግጡ የተለያዩ መፈክሮችን አሰምተዋል፡፡