የሀገር ውስጥ ዜና

ህወሓት በአለም አቀፍ ደረጃ በሽብር የሚያስፈርጁ ሁሉንም ወንጀሎች ፈጽሟል – የህግ ምሁራን

By Feven Bishaw

September 03, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)አሸባሪው ህወሓት በአለም በሽብርተኝነት የሚያስፈርጁ ሁሉንም ወንጀሎች መፈፀሙን የህግ ምሁራን ገለፁ።

በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህር የሆኑት መምህር መሀመድ ሰይድ ÷በስልጣን በቆየበት ዘመኑ ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ሲፈፅም የቆየው ትህነግ አሁን እየፈጸማቸው ያሉ ግፎች በአለም አቀፍ ወንጀል የሚፈረጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።