የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ የአማራ ተወላጅ ባለሀብቶች በአሸባሪው ትህነግ ተፈናቅለው ደሴ ለሚገኙ ዜጎች ድጋፍ አደረጉ

By Feven Bishaw

September 03, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በአዲስ አበባ የአማራ ተወላጅ ባለሀብቶች በአሸባሪው ትህነግ ተፈናቅለው ደሴ ለሚገኙ ዜጎች የአንድ ወር የምግብ ፍጆታ ድጋፍ አደረጉ፡፡

ባለሀብቶቹ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ለአማራ ልዩ ኀይልና ሚሊሻም ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በተወካዮቻቸው አቶ በላይነህ ክንዴና አቶ ደስታ ምህረቴ አማካኝነት ነው ድጋፉን ያበረከቱት፡፡