Fana: At a Speed of Life!

ፈረንሳይ ወደ ሳህል ቀጠና ተጨማሪ ወታደሮችን ልትልክ ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥር 25 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ፈረንሳይ ወደ ሳህል ቀጠና ሃገራት ተጨማሪ 600 ወታደሮችን እንደምትልክ አስታወቀች።

ፓሪስ ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ያላቸው ታጣቂ ቡድኖች በአካባቢው የሚፈጽሙትን ጥቃት ለመከላከል ነው ተጨማሪ ወታደሮችን የምትልከው።

አሁን ላይ ፈረንሳይ በቀጠናው 4 ሺህ 500 ወታደሮች ያሰማራች ሲሆን፥ የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስከበር ቁርጠኛ አቋም እንዳላትም ገልጻለች።

ወታደሮቹም በያዝነው ወር መጨረሻ ወደ ስፍራው ያቀናሉ ተብሏል።

ምንጭ፡-አልጀዚራ

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.