የሀገር ውስጥ ዜና

የተለያዩ ኮሌጆች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች አስመረቁ

By Melaku Gedif

September 04, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋርማ ኮሌጅ እና ጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለየዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቀዋል፡፡

ፋርማ ኮሌጅ 559 ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን÷ከነዚህ መካከልም 359 የሚሆኑት በመጀመሪያ ዲግሪና በደረጃ የተመረቁ ናቸው።