የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ 108 የመገበያያ ቦታዎችናተጨማሪ የግብርና ምርት ተዘጋጅቷል

By Melaku Gedif

September 04, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ 108 የመገበያያ ቦታዎችን እና ከ250 ሺህ ኩንታል በላይ ተጨማሪ የግብርና ምርት መዘጋጀቱን ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል፡፡

በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ የጀመሩት መሸጫዎቹ በከተማችን የሚስተዋለውን የኑሮ ውድነት በማረጋጋት በተለይም የግብርና ውጤት የሆኑ የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን እንዲሁም እንደ እንቁላል ያሉ የእንስሳ ተዋጽኦ አቅርቦትን ይበጥል በማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል።