የሀገር ውስጥ ዜና

የድምፃዊ አለማየሁ እሸቴ ሥርዓተ ቀብር የፊታችን ማክሰኞ ይፈጸማል

By ዮሐንስ ደርበው

September 04, 2021

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 29፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የድምፃዊ አለማየሁ እሸቴ ሥርዓተ ቀብር የፊታችን ማክሰኞ ጳጉሜን 2 ቀን 2013 በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም የአርቲስቱ የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴ አስታወቀ።

የአርቲስቱ የአስክሬን ሽኝት በመስቀል አደባባይ እንደሚከናወንም ተገልጿል።