የሀገር ውስጥ ዜና

የፌዴራል ፖሊስ አባላት፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የፀጥታ አካላት ጁንታው ይዞት የነበረውን ስትራቴጂክ ተራራ አስለቀቁ

By Feven Bishaw

September 05, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በወሎ ግንባር የዘመቱት የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አባላት ከሀገር መከላከያ ሰራዊትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ጁንታው ይዞት የነበረውን ስትራቴጂክ ተራራ ማስለቀቃቸው ተገለፀ ፡፡

አባላቱ በቅንጅት ያስለቀቁት ቦታ በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ በጎሀ ተራራና አካባቢ ሲሆን÷ በስፍራው መሽጎ የነበረውን የአሸባሪውን ህወሃት ጁንታ ቡድን ታጣቂዎችን ባካሄዱት እልህ አስጨራሽ ፍልሚያ የጁንታው ቡድን ታጣቂዎች ላይ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራም አድርሰዋል።