የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ በሁለት ዙር በተካሄደ የፅዳት ዘመቻ 25 ሺህ ቶን ደረቅ ቆሻሻ ማስወገድ ተችሏል

By Feven Bishaw

September 05, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በሁለት ዙር በተካሄደ የፅዳት ዘመቻ 25 ሺህ ቶን ደረቅ ቆሻሻ እና 1 ሺህ ኪሎ ሜትር ፍሳሽ ማስወገጃ ቦይ ማጽዳት መቻሉ ተገለጸ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ በአዲስ አበባ ፅዱ ያልነበሩ የተለያዩ አካባቢዎችን በማጽዳት አሁን ውብና ፅዱ ማድረግ ተችሏል ያሉ ሲሆን ÷እነዚህን ውብ ስፍራዎች እንደተዋቡ እንዲቆዩም ፅዳቱ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል።