የሀገር ውስጥ ዜና

ወጣቱ መከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀል ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጥሪ አቀረቡ

By Feven Bishaw

September 06, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ወጣቱ በከፍተኛ ደረጃ መከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀል ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጥሪ አቀረቡ።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የሰላምና የሕዝብ ደኅንነት ጉዳዮች መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ አሸባሪው የትህነግ ወራሪ ቡድን በስልጣን በቆየባቸው ዓመታት መከላከያ በአንድ ብሔር የበላይነት የተገነባ ነበር ብለዋል።