አዲስ አበባ ፣ ጳጉሜን 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልላዊ መንግስት ህወሓት በክልሉ ወረራ በመፈጸም ንፁሃን አርብቶ አደሮችን እየጨፍጨፍ ቢሆንም ለወንድም የትግራይ ህዝብ ሲባል ህይወት አድን የሰብዓዊ ድጋፍ በክልሉ በኩል እንዲተላለፍ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
የአፋር ክልል መንግስት፣ የፀጥታ አካላት እንዲሁም የጎሳ መሪዎች ከዓለም ምግብ ፕሮግራም ጋር በቅርበት እየሰሩ እንደሚገኙም በመግለጫው አመልክቷል።