አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚገመት ምግብና ቁሳቁስ ከሰሜን ወሎ የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው ደሴ ከተማ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ አደረገ፡፡
ድጋፉን የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገዝሙ ቀልቦ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና ለማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተት ዶክተር ጌታቸው ጉግሳ አስረክበዋል።