የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች መጠን በእጥፍ ጨምሯል

By Melaku Gedif

September 06, 2021

አዲስ አበባ ፣ ጳጉሜን 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2013 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የሳይበር ምህዳር ላይ የተሰነዘሩ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች መጠን በእጥፍ መጨመሩንየኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አስታውቋል።

በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንት ኤጀንሲ ብሄራዊ የሳይበር ጥቃት የአደጋ ዝግጁነት እና ምላሽ መስጫ ዲቪዢን ሃላፊ አቶ ሰብለወይን ጸጋዬ እንደገለጹት÷ በ2013 በጀት አመት ከ2 ሺህ 800 በላይ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ተሰንዝረዋል።