የሀገር ውስጥ ዜና

ወ/ሮ አዳነች ማህበረሰቡን ዝቅ ብለው ለሚያገለግሉ ሰራተኞች ምስጋና አቀረቡ

By Melaku Gedif

September 07, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ጳጉሜ 02 የአገልጋይነት ክብር ቀን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማገልገል ክብር ነው! በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው ፡፡

ቀኑን ምክንያት በማድረግም ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተለይም ዘቅ ብለው ማህበረሰቡን በጽዳት የሚያገለግሉ ሰራተኞችን፣ የእሳት አደጋ ሰራተኞችን እንዲሁም የህዝብን ሰላም ለሚጠብቁ ፖሊሶች እና ደንብ አስከባሪዎችን ምስጋና አቅርበዋል፡፡