አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ጳጉሜ 02 የአገልጋይነት ክብር ቀን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማገልገል ክብር ነው! በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው ፡፡
ቀኑን ምክንያት በማድረግም ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተለይም ዘቅ ብለው ማህበረሰቡን በጽዳት የሚያገለግሉ ሰራተኞችን፣ የእሳት አደጋ ሰራተኞችን እንዲሁም የህዝብን ሰላም ለሚጠብቁ ፖሊሶች እና ደንብ አስከባሪዎችን ምስጋና አቅርበዋል፡፡