የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ ባለሃብቶች ለአፋር ክልል ተፈናቃዮች 100 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ

By Melaku Gedif

September 07, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 2፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ባለሃብቶች በአፋር ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የ100 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ባለሃብቶቹ ያደረጉትን ድጋፍ ሠመራ ከተማ በመገኘት ዛሬ ለአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ አስረክበዋል።