አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 2፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
የዞኑ ፖሊስ የኮሙዩኒኬሽን ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ቶሎሳ ጎሹ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ አደጋው የጭነት አይሱዙ ተሽከርካሪ ከጎሮ ሙጢ ወረዳ ድንችና ሰዎችን አንድ ላይ ጭኖ ወደ ሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማ ሲጓዝ በመገልበጡ የደረሰ ነው፡፡