የሀገር ውስጥ ዜና

የድምፃዊ አለማየሁ እሸቴ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ

By Feven Bishaw

September 07, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 2፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአንጋፋው ድምፃዊ አለማየሁ እሸቴ የቀብር ስነ ስርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ተፈፀመ፡፡

የአርቲስቱ የአስክሬን ሽኝት በመስቀል አደባባይ ከተካሄደ በኋላ የቀብር ስነስርዓቱ ቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ተፈፅሟል፡፡