አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለአዲስ አመት የስጋ ውጤቶችን በጥራትና በተመጣጠነ ዋጋ ለማድረስ ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ገለጸ።
የድርጅቱ የኢንፎርሜሽንና ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል፤ ድርጅቱ ለ2014 አዲስ ዓመት ከ2 ሺህ 500 በላይ የዳልጋ ከብት እና ከ1 ሺህ 500 በላይ በግና ፍየሎችን ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።