የሀገር ውስጥ ዜና

ለአዲስ አመት የስጋ ውጤቶችን በጥራትና በተመጣጠነ ዋጋ ለማድረስ ዝግጅት ተደርጓል-ቄራዎች ድርጅት

By Feven Bishaw

September 08, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለአዲስ አመት የስጋ ውጤቶችን በጥራትና በተመጣጠነ ዋጋ ለማድረስ ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ገለጸ።

የድርጅቱ የኢንፎርሜሽንና ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል፤ ድርጅቱ ለ2014 አዲስ ዓመት ከ2 ሺህ 500 በላይ የዳልጋ ከብት እና ከ1 ሺህ 500 በላይ በግና ፍየሎችን ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።