አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሲሚንቶ ፋብሪካዎችና ከኤክስፖርት ኢንዱስትሪዎች በስተቀር ሌሎች ኢንዱስትሪዎች በበዓሉ ዋዜማ ከዋናው የኃይል ቋት ኤሌክትሪክ እንዳይጠቀሙ ተጠየቀ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበዓሉ በዋዜማና በበዓሉ ዕለት የኤሌክትሪክ ኃይል ሊያጋጥም የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ መቀነስ እንዲያስችል እንዲሁም ከተከሰተም በአፋጣኝ የጥገና ስራ ለማከናወን ቡድን አዋቅሮ የቅድመ ዝግጅት ስራውን ማጠናቀቁ ተገልጿል፡፡