አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳ በሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ማዕከል የመከላከያ ሰራዊት አባላትን አበረታትተው ለተመለሱ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች አቀባበል አደረጉ፡፡
ርሰ መስተዳድሩ ከክልሉ ለተውጣጡ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በተዘጋጀ የአቀባበል መርሃ ግብር ላይ እንደገለጹት÷ በሀገራችን እና በህዝባችን ላይ ያንዣበበውን ጦርነት ለመመከት የክልሉ ህዝብ ያደረገው ድጋፍ ከፍተኛ ነው።