አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሚስራ አብደላ በክልሉ ከሚገኙ የደቡብ ክልል ተወላጆች እና የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
የክልሉ መንግሥት በህብረተሰቡ ዘንድ የሚነሱ የመሰረተ ልማት እና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም ተያያዥ ችግሮችን ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ ተናግረዋል፡፡